ይህ መጽሐፍ በኢትዮጵያ የሀገረ መንግስት ግንባታ ውስጥ ያሉትን ውስብስብ የፖለቲካኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ስነ-ልቦና ስብራቶች በመመርመር፣ “ከፅልመት” ወደ “ብርሃን”ለመሻገር አስቻይ መንገድ ይተነትናል። ጸሀፊው ሀገራዊ ቁስላችንን እያወሳ፣ ሀገር በቀልእሴቶቻችንን ከተራማጅ የፍትህ እሳቤዎች ጋር በማሰናሰል ትውልዱ ከተበዳይነት ትርክትወጥቶ የጋራ አሸናፊነትን፣ የህግ የበላይነትን፣ የሃሳብ ልዕልናን እና የሞራል ከፍታን በማስፈንከማንነታችን የተቀዳ አስተሳሰብ የብርሃን መንገዳችን ስንቅ ሊሆን እንደሚገባ ይመክራል።መፅሀፉ የነገው ብሩህ መንገዳችን የትላንትን ታሪክ እንደ ማነቆ ሳይሆን እንደ መማሪያየሚወስድ፣ ሀገሪቱ በጠንካራ ግለሰቦች ሳይሆን በማይናወጡ ተቋማት ላይ በመገንባት፣ እንዲሁምበጋራ መግባባትና በጥበብ የሚመራ ሊሆን እንደሚገባ አነቃቂ መከራከሪያዎችን ይሰነዝራል።በዚህም፣ የሀገሪቱን ስር የሰደዱ፣ ውስብስብ፣ መዋቅራዊና ግጭት አዘል ቋጠሮዎች ብሩህተስፋ (optimistic)፣ ግልፅ እና ቀላል በሆነ መልኩ (reductionist) የመፍትሔ መንገድማስቀመጡ መጽሐፉን ለአውንታዊ ግምገማ ብቻ ሳይሆን ለአሉታዊ ሙግት ይጋብዛል። ይህንየፀሃፊውን የብርሃን መንገድ ራዕይ ለመረዳት፣ ክርክሩን ለማዳበር፣ ለመሞገት ወይም ሚዛንላይ ለማስቀመጥ እያንዳንዱ አንባቢ መጽሐፉን ወደ ውስጥ ዘልቆ እንዲያነብ እና በጥልቀትእንዲፈትሽ እመክራለሁ።
Please login to view seller contact details.